በ30ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚር ሊግ አርሰናል ኤቨርተንን 2 ለ 0 በማሸነፍ ይበልጥ ወደ ዋንጫው ቀርቧል፡፡
በኤምሬትስ በተደረገው ጨዋታ ተቀይረው የገቡት ቪክቶር ዮኬሬስ 89ኛው ደቂቃ ላይ እና ወጣቱ ማክሰ ዶውማን በባከነ ሰዓት የመድፈኞቹን ዋሳኝ ግቦች አስቆጥረዋል፡፡
የ16 ዓመቱ እንግሊዛዊ ባለተሰጥኦ ወጣት ዶውማን በፕሪሚየር ሊጉ ግብ ያስቆጠረ በዕድሜ ትንሹ ተጫዋች ሆኗል፡፡ ዶውማን ሜዳ ውስጥ በቆየበት 16 ደቂቃ ብቻ አንድ ግብ ከማስቆጠሩ በተጨማሪ አንድ ለግብ የሚሆን ኳስ አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
መድፈኞቹ ሊጉን በ70 ነጥብ ሲመሩ ማንችስተር ሲቲ በ60 ነጥብ ይከተላል፡፡
More Stories
ማንቼስተር ዩናይትድ ከአስቶን ቪላ…
በሴዑል ማራቶን ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ አሸነፉ
በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዛሬ ምሽት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ