February 20, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ዋሽግተን-ጠቅላይ ፍርድ ቤት የትራምፕን የቀረጥ ጭማሪ ደንብ ዉድቅ አደረገ

ማሻ፤ የካቲት 13/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የዩናይትድስ ቴትስ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በተለያዩ ሐገራት ሸቀጦች ላይ የጣሉትን የቀረጥ ወይም የታሪፍ ጭማሪን የሐገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ዉድቅ አደረገዉ።ወግ አጥባቂ ዳኞች የሚበዙበት የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ፕሬዝደንት ትራምፕ የምጣኔ ሐብት አጀንዳቸዉን ገቢር ለማድረግ የሚጠቀሙበትን የሥልጣን መሳሪያ አግዷል።ትራምፕ ሐገራትን በቀረጥ ጭማሪ ለመቅጣት፣ ለመበቀልና የሚፈልጉቱን እንዲያደርጉ ለማስገደድ የሚጠቀሙት የዓለም አቀፍ አስቸኳይ የኤኮኖሚ ሥልጣን (IEEPA) የተባለዉን ደንብ ነዉ።የዩናይትድ ስቴትስ የመጨረሻ ፍርድ ቤት ዳኞች ዛሬ 6 ለ3 በሆነ ድምፅ ባፀደቁት ዉሳኔ ግን ትራምፕ ተጨማሪ ቀረጥ እንዲጥሉ የIEEPA ደንብ ሥልጣን አይሰጣቸዉም።ፕሬዝደንት ትራምፕ የIEEPA በተባለዉ ደንብ መሠረት በየሐገራቱ ላይ እንዳሻቸዉ የቀረጥ ጭማሪ መጣላቸዉን ከዚሕ ቀደም አንድ የአሜሪካ የበታች ፍርድ ቤት «ሕገ-ወጥ» በማለት ቀረጥ መጨመሩ እንዲቆም ወስኖ ነበር።ይሁንና የትራምፕ አስተዳደር ለጠቅላይ ፍርድ ቤት አቤት በማለቱ ዉሳኔዉ አልፀናም ነበር።

#DW Amharic