ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) አርሶ-አደሮች በፍጹም ጽናት፣ ቅንጅት እና ትብብር አካባቢያቸውን የቀየሩበትን ስራ በመመልከታቸው መደሰታቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት አስታውቀዋል።
የተመለከቱት የእርሻ ስራ ፤ የአካባቢ መሬትን እና የውኃ ኃብትን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ትርጉም ያለው ለውጥ ማምጣት እንደሚቻል ማሳያ ነው ብለዋል።
ባህላዊ የመስኖ ዘዴዎችን በመጠቀም እና በቅርብ ያለ ኃብትን በሚገባ ጥቅም ላይ በማዋል ማኅበረሰቡ ውጤታማ እና ተስፋ ሰጪ የግብርና ማዕከል መፍጠር መቻሉን ጠቁመዋል።
በተለይም የመንገድ መሠረተ-ልማት የአርሶ-አደሮችን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ ለማድረስ የፈጠረውን እድል መመልከት እጅግ የሚያበረታታ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
ይኽ እድገት የልማት ጥረቶች ከአካባቢው ማኅበረሰብ ፍላጎት እና አቅም ጋር በቅርበት ሲናበቡ ሊገኝ የሚችለውን ውጤት በግልጽ የሚያሳይ መሆኑንም አመላክተዋል።
More Stories
ሶማሊያ በአሜሪካ ድጋፍ በአል-ሸባብ ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ ዘመቻ ማጠናከሯ ተገለጸ።
ዝነኛው ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሞያ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ በበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ተሸለሙ።
ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ አውሮፕላን ማሪፊያዎች በቅርቡ አገልግሎት ይጀምራሉ