February 18, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው

ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡

ስልጠናው የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ከክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡

በስልጠናው የሁለቱም ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ሰልጠናውን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ ኡሮ አስጀምረዋል፡፡

የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ፣ የመንግስት አስተዳደር ፖሊሲ የትኩረት መስኮችና የያዛቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የስልጠና ሰነድ እያቀረቡ ነው፡፡

#ቦንጋ ኤፍ ኤም