ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ፖሊሲ ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ነው፡፡
ስልጠናው የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ከክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ጋር በትብብር ያዘጋጁት ነው፡፡
በስልጠናው የሁለቱም ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ሰልጠናውን የክልሉ ፋይናንስና ኢኮኖሚ ልማት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መለሰ ኡሮ አስጀምረዋል፡፡
የክልሉ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ፣ የመንግስት አስተዳደር ፖሊሲ የትኩረት መስኮችና የያዛቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የስልጠና ሰነድ እያቀረቡ ነው፡፡
#ቦንጋ ኤፍ ኤም
More Stories
ሶማሊያ በአሜሪካ ድጋፍ በአል-ሸባብ ላይ የምታደርገውን ወታደራዊ ዘመቻ ማጠናከሯ ተገለጸ።
ዝነኛው ኢትዮጵያዊ የፊልም ባለሞያ ፕሮፌሰር ኃይሌ ገሪማ በበርሊን ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ተሸለሙ።
ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ አውሮፕላን ማሪፊያዎች በቅርቡ አገልግሎት ይጀምራሉ