February 18, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ኢትዮ ቴሌኮም ለአፍሪካ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ አስተዋጽኦ የማበርከት ፍላጎት አለኝ አለ

ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ኢትዮ ቴሌኮም ከአገር ውስጥ ገበያ ባለፈ አገልግሎቶቹን በቀጠናው በማስፋፋት ለአፍሪካ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዞ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ የማበርከት ስትራቴጂካዊ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ።

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬሕይወት ታምሩ ከአፍሪካ ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (AFC) ፕሬዚዳንትና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሳማይላ ዙባይሩ ጋር ተወያይተዋል።

በዚህ ወቅትም የተቋሙን ራዕይና ፍላጎት ጠቅሰው፥ ይህን ዕውን ለማድረግ ጠንካራና የረጅም ጊዜ የፋይናንስ አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።

በውይይቱ ወቅት ዋና ሥራ አስፈጻሚዋ ተቋሙ ከዚህ ቀደም የተገበራቸው ስትራቴጂዎች የተቋሙን ጠንካራ የመፈጸም አቅም በተግባር ያረጋገጡ መሆኑን አስረድተዋል

#አራዳ ኤፍ ኤም