ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የነዳጅ ምርት መፈተሻ ላብራቶሪ በድሬዳዋ ከተማ በቅርቡ ልትከፍት መሆኑን የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት አስታወቀ።
የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ላብራቶሪው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ የነዳጅ ምርቶችና ዘይቶች የተቀመጠውን የጥራት መስፈርት ማሟላታቸውን ለመፈተሽ የሚያስችል ነው።
አገልግሎቱ በቅርበት መሰጠቱ አምራች ድርጅቶችና ተቋማት በተቀላጠፈ መንገድ ጥራት ማረጋገጥ እንዲችሉ የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ለዚህም ዘመናዊ መሣሪያዎችና የሰለጠኑ ባለሙያዎች መዘጋጀታቸውን ጠቁመዋል።
ተቋሙ በድሬዳዋ፣ በአዳማ፣ በሐዋሳና በባሕር ዳር ተጨማሪ የፍተሻ ላብራቶሪዎችን በማደራጀት ላይ እንደሚገኝም ነው ያስገነዘቡት
#ጋዜጣ_ፕላስ
More Stories
ኢራን እስራኤል በሊባኖስ ላይ የምታደርሰው ጥቃት የተኩስ አቁም ስምምነቱን ትርጉም አልባ ያደርገዋል አለች
ከግማሽ ክፍለ ዘመን በላይ ኢትዮጵያን በዲፕሎማሲው መስክ ያገለገሉት አምባሳደር ቆንጂት ሥነ ጊዮርጊስ በማረፋቸው የተሰማኝን ኀዘን ለመግለጽ እወዳለሁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዓመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት ገመገሙ