February 18, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ አውሮፕላን ማሪፊያዎች በቅርቡ አገልግሎት ይጀምራሉ

ማሻ፤ የካቲት 11/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) ሦስት አዳዲስ የሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማሪፊያዎች በሚያዚያ ወር ተመርቀው ስራ ይጀምራሉ አለ የኢትዮጵያ አየር መንገድ።

አየር መንገዱ ባወጣው መረጃ÷ በግንባታ ላይ ከሚገኙት የሀገር ውስጥ የአውሮፕላን ማሪፊያዎች መካከል በመጪው ሚያዚያ ወር ሦስቱን በማስመረቅ በረራ ለመጀመር ማቀዱን አስታውቋል።

እነዚህ አዳዲስ መዳረሻዎች ነገሌ ቦረና፣ ጎሬ መቱ እና ደብረ ማርቆስ መሆናቸውንም አመልክቷል።

#ኤፍ ኤም ሲ