ማሻ፤ የካቲት 9/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) መንግስት የኑሮ ዉድነትን ለማረጋጋት አዳዲስ መመሪያ በማዘጋጀትና የተለያዩ ፖሊሲዎችን በመቅረጽ እርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል።
በዚህም የኑሮ ውድነትን በማረጋጋት የማሕበረሰቡን ኑሮ ጫና ማቃለል እንዲያስችል የሰንበት ገበያዎች ተቋቁመው ማሕበረሰቡ ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ ነው።
ሰንበት ገበያው የተለያዩ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን ከአምራቾች ወደ ሸማቹ ቀጥታ በማድረስ የዋጋ ጭማሪን ለመቆጣጠር ያግዛል።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በ2018 በጀት ዓመት ባለፉት ስድስት ወራት የሰንበት ገበያ ማጠናከር ይረዳ ዘንድ 3 ሚሊዮን 845 ሺህ ብር ተመድበው ሥራዎች ሲሰሩ መቆየቱን የክልሉ ንግድና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታውቀዋል
#ሪፖርታዥ
More Stories
የናይጀሪያ ጥቃት
ኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፉን የምትገነባ እና የምትመራ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋትን ለማስፈን የምታደርገውን ያላሰለሰ ጥረት እና የምትከፍለውን መሥዋዕትነትም አድንቀዋል።