የካቲት 9/2018 (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) በስኮትላንድ የግላስጎው የሥነ-ጥበብ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነችው የ22 ዓመቷ ኤሚሊያ ኢቫንስ-ሙንተን፣ የዓለማችን ግዙፉን የጦጣ ቅርጽ ያለው (Sock Monkey) የአሻንጉሊት ቅርፅ በመሥራት ጊነስ ዓለም አቀፍ ክብረ ወሰን ላይ ተመዘገበች።
ይህ ግዙፍ አሻንጉሊት 15 ሜትር ርዝመት ያለው ሲሆን፣ ለሥራውም 60 ሜትር ገደማ የሚረዝም ጨርቅ እና የተለያዩ ግብዓቶች ጥቅም ላይ ውለዋል።
ወጣቷ አርቲስት ሥራውን የሠራችው ትልልቅ ሰዎች ከግዙፉ አሻንጉሊት አንጻር ሲታዩ ራሳቸውን እንደ ሕፃን እንዲቆጥሩና የልጅነት ስሜታቸው እንዲቀሰቀስ ለማድረግ እንደሆነ ገልጻለች።
ይህ ግዙፍ አሻንጉሊትበእንግሊዝ ኖርፎልክ በተካሄደ የጥበብ ፌስቲቫል ላይ ለሕዝብ የቀረበ ሲሆን፣ ጎብኚዎች አሻንጉሊቱን በመንካት እየተጫወቱ እንዲዝናኑ ተደርጓል ሲል የዘገበው ዩፒአይ ነው።
More Stories
የናይጀሪያ ጥቃት
ኢትዮጵያ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዘርፉን የምትገነባ እና የምትመራ እንድትሆን ለማድረግ እየተሰራ ነው – ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ
በኢትዮጵያ የዩናይትድ ኪንግደም አምባሳደር ዳረን ዌልች፣ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ሰላም እና መረጋጋትን ለማስፈን የምታደርገውን ያላሰለሰ ጥረት እና የምትከፍለውን መሥዋዕትነትም አድንቀዋል።