February 12, 2026

Masha Fm Woreda to World

Woreda to World

የክልሉ ምክር ቤት መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።

ማሻ፤ የካቲት 05/2018 ዓ/ም (ማሻ ኤፍ ኤም 103.8) የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 9ኛ መደበኛ ጉባኤ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጅነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) በተገኙበት በታርጫ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።

በጉባኤው÷ የክልሉ መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያው ግማሽ ዓመት የአፈፃፀም ሪፖርት ተወያይተው ማጽደቅ፣ የተለያዩ ረቂቅ አዋጆችንና ድንብ መርምሮ እንደሚያጸድቅ ከወጣው መርሐግብር መመልከት ተችሏል። ዘገባው የክልሉ መ/ኮ ነው